በኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት የመሰብሰቢያ አዳራሽ መጋቢት 20 ቀን 2011ዓ.ም የተደረገውን የውይይት መድረክ ያስተባበሩት በኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት የእንስሳት ብዝሀ ሕይወት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብረሀም አሰፋ እንዳሉት የሸኮ ዳልጋ ከብት ንዑስ ዝርያ ጥበቃና ማሻሻል መማክርት ማቋቋም ያስፈለገበት ዋነኛ ዓላማ የሸኮ ዳልጋ ከብት ንዑስ ዝርያ ጥበቃ፣ዘለቂታዊ አጠቃቀምና የምርምር ሥራዎችን በመደገፍ ዙሪያ የሚሰሩ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ለማሰባሰብና በንኡስ ዝርያው ጥበቃ ላይ የሚሰሩ ሥራዎችን በቅንጅት ማከናወን እንዲቻል ነው ብለዋል፡፡
እንደ አቶ አብረሀም ገለጻ የሸኮ ዳልጋ ከብት ዝርያ ቁጥር በመናመን ላይ የነበረ ዝርያ የነበር ቢሆንም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ በተሰራው ውጤታማ ሥራ ቁጥሩ የተሻለ ደረጃ ላይ መድረሱን ገልጸው ወደ ትክክለኛ ወይም ወደሚፈለገው ቁጥር እንዲደርስ ለማድረግ የዚህ መማክርት መቋቋም እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡